በዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ አስገራሚ ነገሮች ተሰሙ | Zehabesha com
(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ አስቸኳይ ስብሰባ የተቀመጠው የሃገር ቤቱ ሲኖዶስ በዛሬው ውሎው የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ጳጳሳት ፍላጎት በአሸናፊነት ጎልቶ በመውጣት ላይ እንዳለ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከስፍራው ዘገቡ። እንደምንጮቹ ገለጻ ከትግራይ የመጡት ጳጳሳት “አቡነ መርቆርዮስ ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱ ከሆነ ትግራይ የራሷን ፓትርያርክ በመሾም በእርሱ እንመራለን፤ ቤተክርስቲያንንም እንከፍላለን” የሚል አቋማቸውን ማሳየታቸውን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ዘግበዋል። Read more…
የFBI መርማሪዎች አበበ ገላውን ለመግደል የታቀደ ሴራ አከሸፉ – በሴራው የተሳተፉ የህወሃት ሰላዮች ምርመራ እየተደረገባቸው ነው
ታህሳስ ፴(ሰላሳ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ሰሞኑን አንድ የአሜሪካ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ (FBI) ግበረሃል ባለፈው ወር መባቻ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ወደ ቦስተን ለኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተጓዘበት ወቅት የግድያ ወንጀል ለመፈጸም በመዶለትና በማስተባበር ተግባር ላይ ተሰማርቶ የነበረና ለህወሃት መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚሰልል የሚጠረጠር ግለሰብ እና በግብረአበሮቹ ላይ ከፍተኛ ምርመራ መክፈቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጡ።
ሻለቃ ፀአዱና ሟቹ ዶ/ር ልኡል – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ሻለቃ ፀአዱ የህወሓት ታጋይ የነበረች ናት። ከኤርትራና ጣሊያን የዘር ግንድ ያላት ሻለቃ ፀአዱ የቀይ ቆንጆ ናት፤ ገፅታዋን በመመልከት ማንነትዋን በቀላሉ መገመት ይቻላል። የሽማግሌው ስብሃት ነጋ ባለቤት ነበረች። ሽማግሌው ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በአብዛኛው የድርጅቱ አባላት የሚታወቁበት ባህርይ ሴሰኝነታቸው ነው። ከፀአዱ ጋር ከበረሃ የጀመሩት ፆታዊ ግንኙነት እስከ 1990ዓ.ም ድረስ የዘለቀ ሲሆን በ ጊዜያቸው ልጆች አፍርተዋል። በኮንኮርድ ሆቴል ጀርባ ገባ ብሎ በሚገኘው Read more…
የመጨረሻህ መጀመሪያ
በዚህ በውጭው ዓለም ለምንገኘው ለብዙዎቻችን ፥በተለይ ባለፉት 7 እና 8 ዓመታት ላቋቋምናቸው አጥቢያ አቢያተ ቤተክርስቲያናት፥ ምርጫችንን እናት ቤተክርስቲያናት አድርገን ስንጓዝ፥ መንገዱ እንደዚህ እንደ ዛሬው ቀላል አልነበረም፥ የተለያዩ ቅጥያ ስሞች እየተለጠፉብንና በአደባባይም ስንት ነቀፋ እየተቀበልንም ነበር። የወያኔ ቅጥረኞች እና የአባ ጳውሎስ አሽከሮች የሚሉት በተደጋጋሚ የሚዘወተሩ ሲሆኑ አጥቢያ አቢያተ ቤተክርስቲያናቱን ለማህበረ ቅዱሳን አባላት ብቻ እንደ ተቋቋመ የሚመለከቱንም Read more…
የ “አማሮች ገለል በሉ ጉዳይ”: ታሪካዊ ስህተት ታሪክ የማይረሳው ዋጋ ያስከፍላል ከ አምደጺዮን
ሁሉም ነገር ገደብ ያስፈልገዋል። ኢትጵያዊ ትህትና፣ ትዕግስት፣ ይሉኝታ፣ …… እና ሌሎች በመልካም ምግባርነት የሚወደሱ ሰብአዊ ባህሪዎች መልካምነታቸው አጠራጣሪ ባይሆንም ልክ ፣ ገደብ እና ሚዛን ….. ከሌላቸው ግን ስሜት አልባነትን ፣ ሙትነትን ፣ ፈሪነትን፣ ተሸናፊነትን፣ አጎብዳጅነትን …… ማመልከታቸው አይቀርም። Read more…
የትግሬው መንግስት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ት እርቅ እንዲወርድ ሲጥሩ የነበሩትን ሊቀካህናት ኃይለሥላሴን ከሃገር በግዳጅ አስወጣ
ከአገር ሽማግሌዎች ጋራ የተነጋገሩት ልኡካኑ መንግሥትን የመነጋገር ዕቅድም ነበራቸው
የዕርቅና ሰላም ተስፋው ክፉኛ እየተመናመነ ነው
የማክሰኞው የቅ/ሲኖዶስ ጉባኤ በወሳኝነት እየተጠበቀ ነው
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ልኡክ በመኾን ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት ሁለት ልኡካን አንዱ የኾኑት ሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዓለማየሁ ትላንት፣ ታኅሣሥ 19 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት ከኢትዮጵያ እንዲወጡ መደረጋቸው ተሰማ፡፡ Read more…
የትግራይ ንግድ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ራሱን ገነጠለ
የኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባዔ ተራዘመ፣ – የትግራይ ምክር ቤት ራሱን እንዳገለለ ነው
የትግራይ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት የሚደረግለትን ማንኛውንም ዓይነት ጥሪ ባለመቀበል ከብሔራዊ ንግድ ምክር ቤቱ ራሱን ማግለሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በዳዊት ታዬ
የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ኅዳር 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ለማካሄድ አቅዶት የነበረውን አምስተኛውን ጠቅላላ ጉባዔ ከሁለት ወር በላይ አራዘመ፡፡ በወይዘሮ ሙሉ ሰለሞን የሚመራው የምክር ቤቱ የዳይሬክተሮች ቦርድ ከአንድ ወር በፊት አምስተኛውን ጠቅላላ ጉባዔ የሚካሄድበትን ቀን በይፋ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ጠቅላላ ጉባዔው የሚካሄድበት ቀን እንዲለወጥ ቦርዱ ድጋሚ ተሰብስቦ ጥር 16 ቀን 2005 ዓ.ም. እንዲካሄድ መወሰኑን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ Read more…
ሁለተኛው የኢህአዴግ መንግስት
ሁለተኛው የኢህአዴግ መንግስት
አስራት አብርሃም
የሰለሜን ጭፈራ በዓይነ ህሊናችሁ ተመልከቱ። ፊተኛው ወይም መሪው አለንጋውን ይዞ ከኋላው ያሉትን በአለንጋው ሾጥ ሾጥ እያደረገ ጭፈራውን ያስነካዋል። አሁን ደግሞ ሁለተኛው የኢህአዴግ መንግስት የስልጣን ተዋረድ እንመልከትና በሰለሜ ጭፈራ መልክ እንደርድረው። አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከፊት ይሆናሉ። ባዶ እጃቸው ናቸው። አለንጋው የያዘው ሰው ደግሞ ከኋላ ይሆናል፤ ይህ ባለ አለንጋ በአንድ በኩል የህወሀት አርማና የመለስ ምስል ያለው ባርኔጣ ያደረገ ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ በቀኙ ወታደራዊ ኮከብ፣ በግራው “ደህንነት” የሚል ፅሁፍ ያለው ምልክት አድርጓል። Read more…
ሃገር ቤት ባለው ሲኖዶስ የሃሳብ ልዩነት ተፈጠረ
መንግስት ፓትርያርክ ሊያደርጋቸው ካቀረባቸው እጩዎች መካከል አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ብጹእ አቡነ ማትያስ።
(ዘ-ሐበሻ) ትናንት በሰበር ዜና “ኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስ ፓትርያርክ ለመምረጥ አስመራጭ ጳጳትን መረጠ” የሚል ዜና ማስነበባችን ይታወሳል። የሲኖዶሱ ስብሰባ ሳይጠናቀቅ የተወሰኑ አባቶች በተለይ ውጭ ያለው ሲኖዶስ ጋር የሚደረገው እርቀ ሰላም ሳይጠናቀቅ ፓትርያርክ እንዳይመረጥ በመቃወም ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውንና አንዳንድ አባቶችም በስብሰባው ላይ እንዳልተገኙ የዘ-ሐበሻ የቤተክህነት ታማኝ ምንጮች ጠቆሙ። Read more…
የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሥራች፣ የእምዬ ምኒልክ ሀውልት ከመፍረሱ በፊት፣ የአፍራሹ አገዛዝ መፍረስ አለበት!!
ሞረሽ
ዲሰምበር 10 ቀን 2012.
ወዳጅም ጠላትም የመሰከረላቸው፣እምዬ ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ፤የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሥራች ታላቅ አባት መሆናቸውን ነው፡፡ ዐፄ ምኒልክ ገና ከመወለዳቸው በፊት ታላቅነታቸው የተነገረላቸው ናቸው፡፡ ከጥንት ጀምሮ በምኒልክ ስም የሚነግሥ፣ኢትዮጵያን ታላቅ ያደርጋል የሚል ትንቢት ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ንጉሥ ሣህለሥላሴ ሊነግሱ በተዘጋጁበት ወቅት፣ Read more…